ተወዳጆች ሆይ
እንኳን ለወለህ ነቅዐ ሕይወት ጉባኤ ቤት 3ኛ የምሥረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ?
ይህ ቀላል አይደለም
ሁለቱን ዓመታት እንደጸሎተ ሐሙስ ቅዳሴ በውስጥ ቢያከብርም ማለትም
1ኛውን ዓመት በደቀመዛሙርቱ ብቻ ሲያከብር 
2ኛውን ዓመት ደግሞ ከሰቆጣ እና ከአከባቢው የማኅበራትና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተወካዮችን እስከ ጉባኤ ቤቱ ጠርቶ ለማክበር ሞክሯል


3ኛውን ዓመት ደግሞ ጥቂት በጥቂት በማደግ በሰቆጣ ከተማ ከሰኔ አስራ ሰባት እስከ አስራ ዘጠኝ ድረስ በደብረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን  የሕዝብ ጉባኤ በማዘጋጀት የዶግማ የሥርዓት እና የትውፊት ጽንሰ አሳብ ምንድን ነው? የሚለውን ለሕዝብ ግንዛቤ በመስጠት የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ተኩላዎች ምዕመናንን እየጠበቀ ይገኛል፡፡
ከሀገረ ሰብከቱ ሠራተኞች እስከ ወረዳ እና እስከ አድባራት አስተዳዳሪዎች ባለሀብቶችን ጨምሮ ጠቅላላ ጉባኤ በማዘጋጀት በነገው ዕለት ማለትም (ሰኔ 19 /10/) በማኅበረ ቅዱሳን አደራሽ ጥሪ አድርጓል 
የሦስት ዓመት ጠቅለል ያለ አሳብ ይቀርባል ከተጋባዦች አስታየት ተቀብሎ ለበለጠ አገልግሎት ይዘጋጃል፡፡

🌳የሚመስለው የለም🌳
እግዚአብሔር በገናንነቱ ገናና ነው፡፡ በቅዱሳኖቹ የተቀደሰ ነው፡፡ በምስጋናውም የተመሰገነ ነው፡፡
 በክብሩም የከበረ ነው፡፡
ከመቼ ወዲህ የማይሉት ቀዳማዊ ነው፡፡ እስከ ዛሬ የማይሉት ማዕከላዊ ነው፡፡ እስከዚህ የማይሉትም ደኃራዊ ነውና ስለዚህ የሚመስለው የለም፡፡
ለአነዋዋሩ ጥንት የለውም ለአኳሗኑም ፍጻሜ የለውም ለዘመኑ ቁጥር የለውም ለዓመታቱም ልክ ቁጥር የለውምና ስለዚህ የሚመስለው የለም፡፡ ለውርዝውናው ማርጀት የለበትም፡፡ ለኃይሉም ጽናት ድካም የለበትም፡፡ ለመልኩ ጥፋት የለበትም፡፡
ለፊቱ ብርሃንም ጨለማ የለበትምና ስለዚህ የሚመስለው የለም፡፡
ለጥበቡ ባሕር ደንበር የለውም፡፡ ለትዕዛዙም ይቅርታ መስፈርት የለውም፡፡ ለመንግሥቱ ስፋት አቅም ልክ የለውም፡፡ ለአገዛዙም ስፋት ወሰን የለውምና ስለዚህ የሚመስለው የለም፡፡ 
የጥበበኞችን ምክር የሚያጠፋ ጥበበኛ ነው፡፡
የሚመክሩትን ሰዎች አሳባቸውን የሚያስረሳ አዋቂ ነው፡፡
የግብዞችን ፊት የሚያዋርድ ክቡር ነው፡፡
ባልንጀራ የሌለው አንድ ነው ዘመድ የሌለው ሥሉጥ ነው ሰማያት ይጠፋሉ የብስም ትጠፋለች ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃልእርሱ ግን እስከ ዘላለሙ እርስ ነውና የሚመስለው የለም፡፡
ሳይጠይቅ ኅሊናን ይመረምራል ሳይመረምር ልቡናን ይፈትናል ያለመብራት በጨለማ ያለውን ያያል፡፡
ጻድቁን ጽድቅ ሳይሠራ ያውቀዋል፡፡ ኃጥኡንም ኃጢአት ሳይሠራ ያውቀዋል፡፡ ልበኞቹን ከአባታቸው ወገብ ሳይወጡ ያውቃቸዋል፡፡
በደለኞችንም ከእናታቸው ማኅፀን ያውቃቸዋል፡፡
ስለዚህ የሚመስለው የለም፡፡
ለእርሱ ክብር ምስጋና ይድረሰው ለዓለመ ዓለም
ከኤጲፋንዮስ ቅዳሴ የተቀነጨበ
የሊቁ በረከት ይደርብን

 

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 3383

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ

    ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 2634

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 2666

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል

    ...

    Read more: አብርሃም

  • 2654

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት

    ...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 2155

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን

    ...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form