ሰላም ጤና ይስጥልን ተወዳጆች
ይህ በምስሉ የምትመለከቱት የህፃናት ፎቶ በወለህ ነቅዐ ሕይወት የአራቱ ጉባኤያት ትምህርት ቤት የሚማሩት በዕድሜና በሕይወት በእውቀት በሳል የሆኑት አባታችን አባ ገብረ አምላክ በጉባኤ መኖርን መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርገው የያዙ ሲሆን በተጨማሪም የአከባቢውን ህፃናት:- 
ፊደል
ንባብ 
ቁጥር
ምሥጢረ ሥላሴ
ሥርዓተ ቅዳሴ
ሥነ ምግባር ሌላውንም እያስተማሩ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡


ጉባኤ ቤቱም ይህ ተግባር ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅም መሆኑን ተረድቶ ከበጎ አድራጊ ምዕመናን ጋር በመሆን ሥራውን እያበረታታ ይገኛል::
የላቀች ቤተ ክርስቲያንን ለማየት የሚናፍቅ ሁሉ ይህን መንፈሳዊ ጉዞ በተቻለው መጠን ሊደግፈው ይገባል እንላለን ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ድርሻ እንዳለው ካሰበ የማንሠራው ነገር አይኖርም በተለይ በህፃናት ላይ ሳይሠሩ በመሪዎች ላይ ማጉረምረም በራስ ላይ እንደማበድ ነው፡፡
"ህፃናት ላይ ያልሠራች ቤተ ክርስቲያንም ትልቆች አይኖርዋትም"
"ትልቁ የዓለም ሩጫ በህፃናት አእምሮ ላይ ነው"
"ህፃናት ላይ መሥራት ችግኝ ጣቢያ ላይ እንደመሥራት ነው"
"በዚህ ዘመን በህፃናት አእምሮ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት መቻል ብልህነት ነው" እንላለን 
ለህፃናት ሊደረግ ይገባል የምንለው ድጋፍም:-
ኮቸሮ ሳሙና ምንጣፍ ልብስ ሶላር
ሌላውም ነው ይህን እገዛ በማድረግ ማበራታት ያስፈልጋል እንላለን፡፡
ወለህ ነቅዐ ሕይወት ጉባኤ ቤት

ወለህ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ነቅዓ ሕይወት ጉባኤ ቤት  አባታችን እያስተማሯቸው ካሉ ከ 70 በላይ የአካባቢው ሕጻናት  በከፊል።

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 3383

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ

    ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 2634

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 2666

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል

    ...

    Read more: አብርሃም

  • 2654

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት

    ...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 2155

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን

    ...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form