መልካም ዜና
       መምጣት ማየት ነው

የተወደዳችሁ ምእመናን እንደምን አላችሁ? እንኳን አደረሳችሁ?
ዘመናችን በጣም የኦርቶዶክሳውያን ጥቃት እየሰፋ የመጣበት ዘመን ቢሆንም ጨርሰን እንድንጠፋ ያልተወን እግዚአብሔር በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ይበል!
በተለያየ ተፈጥሮአዊም ሆነ ሰው ሰራሽ በሆኑ ችግሮች ውድ ሕይወታቸውን ላጡ ምእመናንም ዕረፍተ ነፍስ ያድልልን?
አሁን ያለንበት ዘመን በቤተ ክርስቲያን ላይ የተደራአበ ፈተና እንደጎርፍ የሚጎርፍበት ዘመን መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ 
ሆኖም ግን ፈተና አለ ብለን መንፈሳዊ ሥራ ከመሥራት መቦዘን አይገባምና በሕይወት እስከአለን ድረስ መንቀሳቀስ የግድ ነው፡፡
በዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት በሰቆጣ ዙርያ ወረዳ በወለህ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ነቅዐ ሕይወት የ፬ቱ ጉባኤ ቤት ከተመሠረተ ሦስተኛ ዓመት የሆነው ሲሆን በእግዚአብሔር ቸርነት በብፁዕ አባታችን መልካም ፈቃድ በሀገረ ስብከቱ ቀና አመለካከት ከሰቆጣ ማዕከል ማኅበረ ቅዱሳን ጋር አንድ በመሆንና በመተባበር በመጀመሪያ ዓመቱ አካሂዶት የነበረውን የተተኪ መምህራን ስልጠና በሀገራዊ ችግር ምክንያት በሁለተኛው ዓመት ማካሄድ ባይችልም ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን በሦስተኛ ዓመቱ እንደገና ለማስኬድ ዝግጅት ላይ ነው፡፡
 በዚህ የስልጠና ቆይታ የሚሰጡ ትምህርቶች:-
1.በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ያለው የመሠረተ ትምህርት ምስጢር 
2.ሥርዓተ ቤተ ክርሽቲያንን መሠረት ያደረጉ የቀቀኖና ትምህርቶች
3.ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት አንፃር የሚተነተኑ ቅብሎሾች
4.ለሰው በጣም አስፈላጊና ዋና የሆነው በዘመናችንም እየከበደ ያለው መንፈሳዊ ትስስር እና ሥነ ምግባራዊ ጉዳይ
5.ከአባቶች እንደ ወረደ ምሥጢረ ሥላሴ የቃል ትምህርት ሆኖ ይቀርባል... ሌላውም በፍቅር ታጅቦ ይሰጣል፡፡
በጣም የሚደነቁበት ደግሞ!
ገና ሲገቡ በመምህራን እግርዎትን ይታጠባሉ፡፡ 
ማረፍያ ይለቀቅልዎታል፡፡
መልካም የሆነ ፊት እያዩ ማዘንዎትን ይረሳሉ፡፡
ከዓለም የወጡ ያህል እስኪሰማዎት ድረስ በመንፈስ ይረካሉ፡፡
ለአንድ ወር ይቀመጣሉ ከተጠቀሙበት የሙሉ እድሜ ስንቅ ይቀስማሉ፡፡
በእውቀት አድገው የአስተሳሰብ ልዕልና አዳብረው በምርቃት ሽኝት እየተደሰቱ ወደበአትዎት ይመለሳሉ፡፡
ይህንንም በተግባር በመግለጽ የሚታይ ሥራ እየሠሩ ለሰማዕትነት ይሽቀዳደማሉ፡፡
ስለዚህ በዞኑም ሆነ ከዞኑ ውጭ ይህን የሚፈልግ ቁጥሩ (30-35) እስኪሞላ አይከለከልም:: ስለሆነም በራሳቸው ወጭ ለምግብ እና ሌሎች ወጮች 3,000 ብር በመክፈል  መሰልጠን የምትፈልጉ  ከወንድም ገ/ሥላሴ(0940832152) እና አሸናፊ(0925017963) እና በየወረዳ ማዕከላችሁ በመደወል እስከ ሐምሌ 04/2014 ዓ.ም  እንድትመዘገቡ። 
ፆታ አይለይም። 
ሥልጠና የሚጀምርበትን ቀን እናሳውቃለን። 
ፎቶ የመጀመርያ ዙር ሰልጣኞች&አሰልጣኞች እና የጉባኤ ቤቱ ገጽታ
( ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!)

 

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 3383

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ

    ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 2634

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 2666

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል

    ...

    Read more: አብርሃም

  • 2654

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት

    ...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 2155

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን

    ...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form