=> ቀን:-   05-11-2013 ዓ.ም
=> ቦታ:-   ነቅዐ ሕይወት(ወለህ ጉባኤ ቤት)
=> መርሀግብር:- የመንፋሳዊ ተቋማት ነባራዊ ህይወትና ልምድ ልውውጥ።

ጠያቂ:- መ/ር ያሬድ
ተጠያቂ(ልምድ አካፋይ):- ዲ/ን ኢሳይያስ  

፩:- የዘመናዊው ሥነ-መለኮት አስተምህሮና የሥርዓት እንዲሁም የትሕርምት ሕይወት ምን ይመስላል?

፪:- የቴዎሎጂያን እና ኮሌጅ የንባብ ባህል ምን ይመስላል?

፫:- ለጉባኤ ቤት ያለን አመለካከት፣ ለሕዝብ ማድረግ ስላለብንና ለዋግ አገረ ስብከት ምን መሥራት አለብን ብለህ ታስባለህ(እናስባለን)?

        *** መልስ ***
፩:- በዘመናዊ አስተምህሮ ያለን እይታ የተሻለ እንዲሆን አለማቀፋዊ የሆኑ ታሪኮችና የተለያዩ ቤተ እምነቶች ስነ-መለኮታዊ እይታ በመማርና ማስተማር በቅድመ ትምህርት መጀመሪያ አመት ከሚማሩት አስተምህሮዎች ዋነኞቹ እንደሆኑ በማብራራት የአስተምህሮውን ስፋትም ከዝርዝር ይዘቶቹ ጋር በአጭሩ ለመግለጽ ሞክረዋል።

፪:- የንባብ ባህልን በሚመለከት ዲ/ን ከተናገራቸው መካከል በጥሩ መንገድ ሊታይ የሚገባው ነገር የንባብ ባሕልን የሚያዳብሩበት በመጽሐፍ የታጨቀ ቤተ-መጽሐፍት መኖር ጎልቶ የተመዘገበ ሲሆን እንደ ፈተና ኦርቶዶክሳዊና ኢ-ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች የሚያስተናግዱ መጽሐፍት መኖር ከአለማቀፋዊ እውነት እና ትምህርት አንፃር ለጥናት ተብሎ ቢታሰብም ለአንጻራዊ ስነ-መለኮታዊ ትምህርት አና ጥናት ሲባል መሠረት የሌላቸውን የቲዮሎጂ ተማሪዮች ከማነጽ ይልቅ የሚያጠፉበት አጋጣሚዎች እንዳሉም በማሰብ ጥንቃቄ ላይ ትልቅ ትኩረት መስጠት እንዳለብን በውይይቱ ምክረሀሳብ ተጠናቋል።

፫:- ቲዮሎጂያን ለጉባኤ ቤት ፣ጉባኤ ቤቱ ለቲዮሎጂያን ያለውን አመለካከት በሰፊው ታይቶ ምክረሀሳቦችም ቀርበው ውይይቱ ተጠናቋል።
ለሁላችሁም(ለሁላችንም) እንኳን አደረሳችሁ/ሰን።
መልካም!

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 3383

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ

    ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 2634

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 2666

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል

    ...

    Read more: አብርሃም

  • 2654

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት

    ...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 2155

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን

    ...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form