ሰላም ጤና ይስጥልን ቸር አላችሁ?
ሰላመ እግዚአብሔር አይለያችሁ?
ጉባኤ ቤታችሁ ወለህ ከጊዜ ወደጊዜ አዳዲስ ነገሮች እየፈጠረ ለሰው የቆመ ትልቅ የርዕይ ባለቤት መሆኑንን እያሳየ ይገኛል፡፡
ደግሞ ምን ተገኘ? የሚል ካለ

በየዓመቱ የሚሰጠው የክረምት ተተኪ መምህራን ሥልጠና እንዳለ ሆኖ 
በዚህ በ2015 ዓ.ም ደግሞ ለወጣቱ እየ ሰጠ ያለውን የዕቅበተ አእምሮ ትምህርት በሕፃናት ላይ መሥራት  አስቦ በከተማ አስተዳደሩ ትምህርት  ቢሮ መልካም ፈቃድ አግኝቶ ለሙከራ ያህል ከ3ኛ እስከ6ኛ ክፍል  ያሉ 120 ሕፃናትን በሥነ ምግባር በግእዝ ቋንቋና በአብነት ትምህርት ዙሪያ ለማስተማር ምዝገባውን 
የጀመረ መሆኑን ስናሳውቅ በደስታ ነው ምን መሆን እንዳለባቸውና እንዴት መሠራት እንዳለበት ያላችሁን አሳብ ለግሡን ለመፈፀም ዝግጁ ነን፡፡
ሁላችንም እንዲህ የቻልነውን በመሥራት እንመን እንጂ  በመንቀፍ የሚመጣ ለውጥ እንደሌለ እያየን ነው፡፡
ሕፃናት ላይ ባልተሠራበት ምንም ለውጥ አይጠበቅም፡፡
በተሠረቀ አእምሮ ምንም መሥራት ስለማይቻል በአእምሮ ጥበቃ ላይ አጥብቀን እሥራ እላለሁ በየ ቤታቸሁ ሰላም ይግባ፡፡
 በፀጋ ጎልምሱ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ እንጂ ለሆድ አትገዙ፡፡
ሰላም

ይህ በዋግ ኽምራ ዞን አስተዳደር አደራሽ የሚሰጠው የዕቅበተ አእምሮ ጉባኤ ነው በቅርብ ካሉ እንዳይለዩ አደራ፡፡
"የምንሞትለት ዓላማ ከሌለን የምንኖርለት ዓላማ አይኖረንም፡፡"
ለምን እንደምትኖር አስብ ያኔ ሁሉም ግልፅ ይሆናል፡፡

 

ይህ የምታዩት የገጠሩን ምእመን ከተኩላ ለመጠበቅ ማይ ጉንዶ በተባለች ቀበሌ የተደረገ ጉባኤ ነው ሃይማኖታውያን  የሆኑት የዋግ ምእመናን የተፈጥሮ አደራሽ በሆነው በዋግ ዋርካ ስር ቁጭ ብለው ጊዜን ባለመሳሳት የተወደደች ሃይማኖታቸውን እየተማሩ ይታያሉ፡፡ 
መንፈሳዊ ቅንዓት ካለ የግድ ምቹ ቦታ አያስፈልግም ሰው በተገኘበት እየተገኙ ወንጌልን ማስፋፋት ይቻላል ምንም ትራንስፖርት ባይኖር የድምፅ ማጉሊያ ባይዘጋጅም በእግር ተጉዘህ በድምፅ ጩኸህ መልእክትህን ትወጣለህ፡፡
ይህ አሁን ባለፈው እሑድ የተደረገ ጉባኤ ነው፡፡
 አንጀት በሚበላ ትምህርቱን ሲቀበሉ ጭራሽ ድካም አይሰማንም፡፡
የቀረንን ነገር አሟልተን በዘመነ መልኩ ለሕዝቡ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ግን መስተካከል ያለበት ቢኖር፡-
1.የእጅ ማይክ
ማለትም ብዙ ሰው ሲሰበሰብ መድረሽ እየተቻለ ስላልሆነ ተንቀሳቃሽ ማይክ ያስፈልገናል 
2.የትራንስፖርት ጉዳይ 
ይህም ሲባል ጉባኤ ቤቱ የራሱ መኪና ሊኖረው ይገባል ነው ከሠራን ይሆናል ቆርቆሮ አይደል?  
3.ሌሎች ነገሮችን
ማለትም ይህ ያስፈልጋችሗል የምትሉትን ሁሉ በመተባበር አቅርቡ ለግል ጉዳይ  አንጠይቅም ለኅብረት ከመጠየቅ የሚከለክለን የለምና እናሳውቃለን፡፡
እኛ አአምሮ ላይ እንሥራ እናንተ ቁስ ላይ ሥሩ በዋጋው ጊዜ እንገናኛለን፡፡
ለውጥ ማየት የናፈቀው ጉባኤያት ይሥራ በዚሁ መቀጠል የፈለገ በህንፃ ላይ ይሥራ፡፡
ሰላም እንገናኝ!!!

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 3383

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ

    ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 2634

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 2666

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል

    ...

    Read more: አብርሃም

  • 2654

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት

    ...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 2155

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን

    ...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form